‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል ተመርቷል

‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል ተመርቷል

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መመረቱን አስታወቀ።

‎የኮርፖሬት ፕላኒግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 29 ሺህ 381 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 27 ሺህ 105 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል።



‎ይህም የዕቅዱ 92 ነጥብ 4 በመቶ መሳካቱን የሚያሳይ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል የ27 ነጥብ 3 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል።

‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከመነጨው ኃይል ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 50 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስትና የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የ18 ነጥብ 3 በመቶ እና የ6 ነጥብ 9 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ተጠቅሷል።

‎በበጀት ዓመቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጨምሮ የአይሻና የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ኦፕሬሽን በመግባታቸው የማመንጨት አፈጻጸሙ የተሻለ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሰዋል።


‎የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች ሲከናወኑ እንዲሁም በማዕቀፍ ግዥ ጭምር የመለዋወጫ ዕቃዎች ሲቀርቡ መቆየታቸውን አንስተዋል። 

‎በቀሪ ሦስት ወራት የግድቦችን ደህንነት በማረጋገጥ እና የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እንዲሁም አማካይ የኃይል ጭነትን በማሻሻል የታቀደውን ዓመታዊ የኃይል ምርት ግብ ለማሳካት እንደሚሰራ አቶ ያለው አይቀር ተናግረዋል::

‎ከመነጨው ኃይል ውስጥ 24 ሺህ 970 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል መሸጡንም ጠቁመዋል።

💡 “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”

Scroll to Top