የደቡብ 1 ሪጅን ሠራተኞች እና አመራሮች 50 ኛውን ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን በዓል አከበሩ።
በበዓል አከባበሩ ላይ ኢንጂነር ምትኩ ንጉሴ እንደተናገሩት ማርች 8 በዓለም ዙሪያ ያሉ ሴቶች ስኬት ፅናት እዲሁም ለእኩልነት የሚደረግ ቀጣይ ትግል የሚታወስበት ቀን በመሆኑ ከካላንደር በላይ የሆነ ኹነት ነው።
ሴቶች ያላቸውን እምቅ ችሎታ ለመጠቀም እና ለተቋም ዕድገት የበኩላቸው ን አስተዋጽኦ ለማሳደግ እንዲችሉ አወንታዊ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ዳይሬክተሩ የሴቶችን ተሳትፎ ከፍ በማድረግ እያንዳንዷ ሴት ህልሟን በነጻነት የምትኖርበት ዓለም መፍጠር የጋራ ኃላፊነታችን ነው ብለዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ የስርዓተ ፆታ ግንዛቤ ማስጨበጫ ጸሁፍ አቅረዋል።
ተቋሙ ሴቶችን ለአመራርነት ማብቃት አወታዊ ድጋፍና ማበረታቻ እያደረገ መሆኑን ገልጸው ሴቶች ያለባቸውን ድርብርብ ኃላፊነት በመቋቋም ራሳቸውን ለስኬት ማዘጋጀት እንዳለባቸው ወ/ሮ ሌንሴ አሳሳበዋል።


