በበጀት ዓመቱ ከ35 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መንጭቷል

በበጀት ዓመቱ ከ35 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መንጭቷል

‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ከ35 ሺህ 670 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨቱን የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ።

‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ 38 ሺህ 124 ነጥብ 78 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 35 ሺህ 670 ነጥብ 99 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል።


‎‎ይህም የዕቅዱን 93 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑንና ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል ጋር ሲነፃፀር የ21 በመቶ ዕድገት ያለው መሆኑን አብራርተዋል።

‎እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ኃይል ውስጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 51 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስት እና የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የ17 ነጥብ 8 እና የ7 በመቶ ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው አንስተዋል።

Scroll to Top