ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ በ7ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን ገጥሞ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሁለተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።
ሁለቱ ቡድኖች በድሬዳዋ ስቴዲየም ዛሬ ባከናወኑት ጨዋታ አቤል ሀብታሙ፣ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ እና ያሬድ የማነ ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሶስቱን የማሸነፊያ ጎሎች አስቆጥረዋል።



ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደጉትን ሁለት ጎሎች አንጋፋው አጥቂ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል።
ብርቱ ፉክክር በታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመስመር ላይ የተመሰረተ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲከተል ፋሲል ከነማ በአንፃሩ ኳስን በመቆጣጠር የጨዋታ ብልጫ ለመውሰድ ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀርቷል።
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ በሊጉ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
? “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”



