ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አቻ ተለያይቷል

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አቻ ተለያይቷል

ድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ባለው የኢትዮጵያ የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከነማ ጋር ነጥብ ተጋርቷል።

ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት የተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ያለምንም ግብ ተጠናቋል።

ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በተደጋጋሚ ሙከራ በማድረግ ድሬዳዋ ከነማ የተሻለ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአንፃሩ በመልሶ ማጥቃት ጎል ለማግኘት ጥረት ሲያደርግ ተስተውሏል።

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ ኢድሪሱ አብዱላሂ በርካታ ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን በማዳን ክለቡን ታድጓል።

ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ14 ነጥብ መቻልን ተከትሎ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በጊዜያዊነት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

በ10ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከስሁል ሽረ ጋር የሚጫወት ይሆናል።

? “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”

Scroll to Top