በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ዛሬ በተከናወነ የ6ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ ለባዶ ተረቷል።
የንግድ ባንክን ብቸኛ የማሸነፊያ ጎል ብርቱካን ገ/ክርስቶስ በ27ኛው ደቂቃ አስቆጥራለች።


በጨዋታ የበላይነት የነበረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በርካታ ግብ ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን ቢያገኝም በሚያስቆጭ ሁኔታ ዕድሎቹን አምክኗል።
በአንፃሩ ንግድ ባንኮች ያገኘውን ብቸኛ ዕድል ወደ ጎል በመቀየር ማሸነፍ ችሏል።
በ7ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም ይጫወታል።
? “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”


