በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው 4ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ – ኤሌክትሪክ ባህር ዳር ከተማን 1 ለባዶ በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ኢትዮ – ኤሌክትሪክ በ16ኛው ደቂቃ ላይ አቤል ሀብታሙ ባስቆጠራት ጎል የመጀመሪያውን አጋማሽ መምራት ችሏል፡፡
ለማሸነፍ ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ባህርዳር ከተማ ቢሆንም ኢትዮ – ኤሌክትሪክ ያገኘውን ዕድል ወደግብ በመቀየር 3 ነጥብ ይዞ ወጥቷል፡፡
ኢትዮ – ኤሌክትሪክ በውድድር ዘመኑ 4 ጨዋታዎችን አድርጎ በሁለቱ አቻ ሲወጣ፣ በአንዱ ተሸንፎ የዛሬውን ጨዋታ አሸንፏል፡፡
ሁለቱ ክለቦች ከዚህ በፊት በተገናኙባቸው ሁለት ጨዋታዎች ባህርዳር ከተማ ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡
? “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”



