የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች

📌 ሀገራዊ የኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት ደርሷል። ይህም በ2017 ከነበረበት በ1 ሺህ 811 ሜጋ ዋት ወይም በ23 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

📌 በበጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ የአይሻ ሁለት እና የአሰላ የንፋስ ኃይል  ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ወደ ኦፕሬሽን ማስገባት ተችሏል።

📌 በ2018 በጀት ዓመት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 124 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል። ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ57 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ አለው።

📌 ከዚህ ውስጥ 475 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ዶላር ገቢ ሲሆን ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ27 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

📌 ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ  ከዕዳ ወጥቶ 39 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘት ችሏል።

📌በበጀት ዓመቱ 38 ሺህ 124 ነጥብ 78 ጌጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዶ 35 ሺህ 670 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል አመንጭቷል።

📌 ከዚህ ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የ51 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ አለው።

📌 ከመነጨው ኃይል ውስጥ 33 ሺህ 24 ነጥብ 59 ጊጋ ዋት ሰዓት የኃይል ሽያጭ ተከናውኗል።

📌ከዚህ ውስጥ 93 ነጥብ 5 በመቶ ለሀገር ውስጥ እንዲሁም 6 ነጥብ 5 በመቶ ለውጭ ሀገራት የቀረበ ነው። ይህም ተቋሙ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ቅድሚያ እየተሰጠ ለመሆኑ ማሳያ ነው።

📌ከሽያጭ ከቀረበው ኃይል ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 56 ነጥብ 41 በመቶ፣ የዳታ ማይኒንግ 32 ነጥብ 51 በመቶ፣)  ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች 4 ነጥብ 24 በመቶ ፣ ለኬኒያ የ4 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም ለጅቡቲ  1 ነጥብ 65 በመቶ የቀረበ ነው።

📌 18 የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን  በተለያዬ የግንባታ ምዕራፍ ላይ ይገኛሉ።

📌 ከፕሮጀክት አስተዳደር፣ ከካሳ ክፍያ፣ ከሎጂስቲክስና ከፀጥታና ስርቆት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በበጀት ዓመቱ ለተቋሙ ተግዳሮቶች እንደነበሩ አንስተዋል።

Scroll to Top