የፕሮጀክት ውጤት
ፕሮጀክቱ ከገናሌ ሶስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሚመነጨውን ኃይል በይርጋለም፣ ወላይታ ሶዶ እና ሀዋሳ ከተሞች ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ወደ ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ጣቢያ ኃይል እንዲተላለፍ ለማድረግ የተገነባ ነው፡፡ይህ ፕሮጀክት በይርጋለም እና ወላይታ ሶዶ ከተሞችና በአቅራቢያቸው የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን እና የሀገር ውስጥ ደንበኞችን በ400 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ለማስተሳሰር ይሰራል።