የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት ላይ ላይ ከተደቀኑት ፈተናዎች መካከል አንዱ የወሰን ማስከበርና ካሳ ክፍያ ችግር ነው፡፡ የወሰን ማስከበር ሥራ በወረዳ እና ከተማ አስተዳደሮች የሚከናወን ሥራ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራውን ከመከታተልና ከመታዘብ ባለፈ ያለው ሚና አነስተኛ ነው፡፡ ይሁንና የወሰን ማስከበር ሥራ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዳይከናወኑ በማድረግ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው፡፡