ፕሮጀክቱ ሁለት አምቡላንሶችን በስጦታ እና በግዥ ማሟላቱን ገለፀ

Published by corporate communication on

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ለሚከሰት የኮቪድ 19 እና ሌሎች የጤና ሥጋቶች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያግዙ አንቡላንሶች መሟላታቸውን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለፁ፡፡

ለፕሮጀክቱ አንዱን አምቡላንስ በስጦታ ሌላኛውን አምቡላንስ ደግሞ በግዥ እንዲሟሉ ያደረገው የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር መሆኑን ኢንጂነር ክፍሌ ገልፀዋል፡፡

ይህም በግድቡ ግንባታ ወቅት ለሚያጋጥሙ የኮቪድ 19 እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ሥጋቶች ፈጣን የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት ያስችለናል ብለዋል፡፡

የሁለቱ አምቡላንሶች ዋጋ 2 ነጥብ 63 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጣ በመግለፅ ለተደረገው ድጋፍ የጤና ሚኒስቴርን አመስግነዋል፡፡

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

eighteen − 15 =