ፕሮጀክቱ ሁለት አምቡላንሶችን በስጦታ እና በግዥ ማሟላቱን ገለፀ
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ለሚከሰት የኮቪድ 19 እና ሌሎች የጤና ሥጋቶች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያግዙ አንቡላንሶች መሟላታቸውን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለፁ፡፡
ለፕሮጀክቱ አንዱን አምቡላንስ በስጦታ ሌላኛውን አምቡላንስ ደግሞ በግዥ እንዲሟሉ ያደረገው የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር መሆኑን ኢንጂነር ክፍሌ ገልፀዋል፡፡
ይህም በግድቡ ግንባታ ወቅት ለሚያጋጥሙ የኮቪድ 19 እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ሥጋቶች ፈጣን የአምቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት ያስችለናል ብለዋል፡፡
የሁለቱ አምቡላንሶች ዋጋ 2 ነጥብ 63 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጣ በመግለፅ ለተደረገው ድጋፍ የጤና ሚኒስቴርን አመስግነዋል፡፡
0 Comments