የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዓለምአቀፍ ትኩረት ስቧል

Published by corporate communication on

የኤሌክትሪክ ዘርፍ ተሸላሚው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለሁሉም ለማዳረስ እገዛ እያደረገ መሆኑን ፓወር የተሰኘው በኃይል ላይ በማተኮር የሚዘጋጀው ዓለምአቀፍ መጽሔት ዘግቧል፡፡

ከህዝቦቿ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኤሌክትሪክ የማያገኙባት ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ አቅርቦት እየተሻሻለች መምጣቷን መጽሔቱ በዝርዝር አትቷል፡፡

መፅሔቱ ይፋ እንዳደረገው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት መንግስት እ.ኤ.አ እስከ 2025 በመላው ሀገሪቱ ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት የሚደረገውን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እገዛ ማድረግ ጀምሯል፡፡

በ3 ተርባይኖች 254 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ተመርቆ ስራ የጀመረው በተያዘው ዓመት አጋማሽ ላይ ነበር፡፡

ይህን ማስፈንጠሪያ በመጫን ዝርዝር ዘገባውን ማግኘት ይችላሉ፡፡

https://www.powermag.com/award-winning-hydropower-project-helps-electrify-ethiopia/

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

20 + nineteen =