የኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ እውነታዎች

Published by biniyam melese on

  • ፕሮጀክቱ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በኮንታ ልዩ ወረዳ እና በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳ መካከል ይገኛል::
  •  ከአዲስ አበባ በጅማ መስመር 540 ኪ.ሜ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ መስመር 560 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል::
  •  ግድቡ ከጊቤ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ129 ኪ.ሜ ያህል ይርቃል::
  • የግድቡን ግንባታ ለማስጀመር የኮንትራት ሥምምነት የተካሔደው መጋቢት 19 ቀን 2008 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ በመጋቢት 28 ቀን 2016) ነው::
  • የግድቡ አይነት- የአርማታ ሙሌት (Roller Compact Concrete)
  • የግድቡ ቁመት – 170 ሜትር
  •  የግድቡ ርዝመት ወደ ጎን – 990 ሜትር
  • የግድቡ ውሃ የመያዝ አቅም – 6,500 ሚሊዬን ሜትር ኪዩብ
  •  የተፋሰሱ ስፋት – 44,325 ካሬ ኪ.ሜ
  •  ግድቡ የሚፈጥረው ሃይቅ ስፋት – 100 ካሬ ኪ.ሜ
  • የማመንጨት አቅም- 2,160 ሜጋዋት
  • ዓመታዊ የኃይል ምርት አቅም – 6,460 ጊጋ ዋት በሰዓት
  • 8 ተርባይኖች የሚገጠሙለት ይሆናል::
  • 3 የውሃ ማስገቢያ (Penstock) ቱቦዎች ይኖሩታል::
  • 20 ሜትር ስፋት እና 17 ሜትር ቁመት ያለው ባለ 6 የውሃ ማስተንፈሻ (Spillway) ቱቦዎች አሉት::
  •  የግድቡን ግንባታ የሚያከናውነው የጣሊያኑ ሳሊኒ ኢምፕሪጅሎ ኤስ.ፒ.ኤ (Salini Impregilo SPA) ኩባንያ
  •  የፕሮጀክቱ አማካሪ የቤልጀሙ ትራክቴብል ኢንጅነሪንግ (Tractebel – Engie)
  •  አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ወጪ – 2.5 ቢሊዬን ዩሮ

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

7 + twenty =