የአይኤስኦ የጥራት ሥራ አመራር (ISO Quality Management) ሥልጠና እየተሰጠ ነው

Published by corporate communication on

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የአይኤስኦ የጥራት ሥራ አመራር (ISO Quality Management) ሥልጠና በመውሰድ ላይ ይገኛል፡፡

ሥልጠናው ሥራ አመራሩ ከጥራት ማኔጅመንት ጽንሰሐሳብ ጋር እንዲተዋወቅ፤ ዓለምአቀፍ አሰራሮችን እንዲረዳና የኦፕሬሽን ቅልጥፍና እንዲያመጣ እንዲሁም የደንበኞችን እርካታ እንዲያሳድግና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲያመጣ ያግዛል ተብሏል፡፡

በስልጠናው ላይ  የአይኤስኦ የጥራት ሥራ አመራር ጽንሰሐሳብ፣ መርሆዎችና ጥቅም፣ ሂደትና ስጋት ሥራ አመራር ላይ ትኩረት ያደረጉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተደርጓል፡፡

ሥልጠናውን በመስጠት ላይ የሚገኘው በዓለም አቀፍ ደረጃ የኦዲት፣ የታክስና የማማከር አገልግሎት የሚሰጠው KPMG ዓለምአቀፍ ነው፡፡

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

twelve − 11 =