የአሉቶ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሚያዝያ 10 የጉድጓድ ቁፋሮው ይጀመራል

Published by corporate communication on

የአሉቶ ላንጋኖ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሚያዝያ 10 ቀን 2013 ዓ/ም የጉድጓድ ቁፋሮ እንዲጀመር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ አቅጣጫ አስቀመጡ።

ለሥራው መጀመር የውሃ አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ ቀሪ ስራዎቹ  በፍጥነት እንዲጠናቀቅም ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ንጉሴና ፕሮጀክቱን በፋይናንስ የሚደግፈው የዓለም ባንክ ተወካዮች እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን በስፍራው በመገኘት ገምግመዋል።

የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት 7 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ 70 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል።

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

3 × two =