የታላቁ ህዳሴ ግድብ የጀነሬተር አንቀሳቃሽ አካል( Rotor) የማስቀመጥ ሥራ ዛሬ በስኬት ተከናወነ

Published by corporate communication on

በቅርቡ ኃይል እንደሚያመነጭ ከሚጠበቁት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለት ዩኒቶች መካከል በዩኒት 10 ላይ  የተርባይን ጀነሬተር ተሽከርካሪ አካል (Rotor) በቦታው ላይ የማስቀመጥ ሥራ ዛሬ በስኬት ተከናውኗል።

ሮታሩና አብረው ያሉት አካላት 840 ቶን ክብደት ያላቸው ሲሆን ሮተሩ ብቻውን 780 ቶን ይመዝናል።

ሮተሩ ከአንድ ጫፍ እስከሌላኛው ጫፍ ድረስ ያለው አጋማሽ ርዝመት ወይም ዳያሜትር 11 ነጥብ 7 ሜትር ነው።

የሮተሩና የተርባይን አካላቶች በአግባቡ መገጠም የኃይል ማመንጨት የሙከራ ስራ ለመጀመር መቃረቡ አመላካች ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

ten − eight =