ዋና ሥራ አስፈፃሚው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል

Published by corporate communication on

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ  ለመላው የድርጅቱ ሠራተኞችና አመራሮች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው በመልዕክታቸው የግድቡን ቀሪ ስራ ለማጠናቀቅ በቀጣይ ፈታኝ ሥራዎች የሚጠበቁ  በመሆኑ ሥራው በታላቅ ቁርጠኝነት እና ትጋት እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የፕሮጀክቱን ማኔጅመንት፣ ተቋራጮችና አማካሪዎች እንዲሁም ከሁሉም በላይ ሳምንቱን ሙሉ ቀንና ለሊት  24 ሰዓት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እየሰሩ ፕሮጀክቱን ለዚህ ስኬት ያበቁ  ሰራተኞችን  አመስግነዋል።

ለፕሮጀክቱ እውን መሆን ህይወታቸውን መስዋዕት ያደረጉ ሰራተኞችንም ተቋሙና ህዝብ ፕሮጀክቱ ጋር ሲያስታውሳቸው እንደሚኖር ጠቅሰዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለፕሮጀክቱ ስኬት  ለሰጡት አመራር፣ ክትትልና ድጋፍ ምስጋና ይገባቸዋል ያሉት ሥራ አስፈፃሚው ለውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ እና ለመከላከያ ሠራዊትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

eleven + 9 =