አዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለጊዜው አገልግሎቱን አቋረጠ

Published by corporate communication on

በአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ በማጋጠሙ ከቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ጣቢያው ለጊዜው አገልግሎት ማቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ II እና III ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዲሳሳ ገልሜሳ አስታውቀዋል፡፡

ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሟል፡፡

ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ በመዋጣቸው የጉዳቱን መጠን ለማወቅ እንዳልተቻለ አቶ ዲሳሳ ተናግረዋል፡፡

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

nineteen − ten =