ለግድቡ በየደቂቃው በአማካይ 17 ዶላር እየተሰበሰበ ነው፤ በአምስት ቀን ውስጥ ከ111 ሺህ ዶላር በላይ ተሰብስቧል

Published by corporate communication on

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚደረግበት ድረ ገፅ www.mygerd.com ይፋ ከሆነ ዛሬ አምስተኛ ቀኑ ነው፡፡

እስካሁን ድረስ ከ876 ኢትዮጰያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ 111,540 ዶላር  ተሠብስቧል ። 45 ሰዎች ደግሞ ለልገሳው የሚሆን ዘመቻ በማድረግ ላይ ናቸው።

በአማካይ በየሰዓቱ 1 ሺህ ዶላር ለግድቡ እየተለገሰ ሲሆን በየደቂቃው ደግሞ 17 ዶላር መሰብሰብ ተችሏል፡፡ እንዲህ ዓይነት የድጋፍ ማሰባሰቢያ ፕላትፎርም ሲዘጋጅ በኢትዮጵያ ይህ የመጀመሪያው እንደሚሆን እምነት አለን፡፡

www.mygerd.com   ድረ-ገፅ   በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሉበት አካባቢ ሆነው ለታላቁ  የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ  ድጋፍ ለማድረግ እና  አሻራቸውን ማሳረፍ ለሚፈልጉ የተዘጋጀ   ድረ-ገፅ   ነው ፡፡

የማይደበዝዝ አሻራዎን ያሳርፉ፤ ሌሎችንም እንዲሳተፉበት ይጋብዙ!!

Categories: ዜና

0 Comments

Leave a Reply

Avatar placeholder

Your email address will not be published.

10 − 9 =